መልስ - በነብዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እና በባልደረቦቻቸው ጊዜ ያልነበረ ሰዎች በሃይማኖት ላይ የፈለሰፉት አዲስ ፈሊጥ ሁሉ ቢድዓህ ይባላል።
* ላመጣው ሰው እንመልስለታለን (እናወግዘዋለን) እንጅ አንቀበለውም።
ምክንያቱም ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እንዲህ ስላሉ፡- "ቢድዓ (አዲስ ፈሊጥ) ሁሉ ጥመት ነው።" አቡዳውድ ዘግበውታል።
ለምሳሌ፡- በዒባዳ ላይ መጨመር: ውዱእ ላይ ለአራተኛ ጊዜ ማጠብ እና የነብዩን የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ልደት (መውሊድ) ማክበርን ፤ ይህ ሁሉ ተግባር ከነብዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ይሁን ከባልደረቦቻቸው የተገኘ ምንም መሰረት የለውም።