መ - 1- በላቀው አላህ ማመን
2 - በመላእክቱ ማመን
3- በመጻሕፍቱ ማመን
4- በመልዕክተኞቹ ማመን
5 - በመጨረሻው ቀን ማመን
6- በቀደር መልካምም ሆነ መጥፎ በሆነ (የአላህ ቅድመ ውሳኔ) ማመን ናቸው።
ማስረጃውም፡- ጂብሪል ዐለይሂ ሰላም ነቢዩን - የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን - ስለ እምነት የጠየቀበት የታወቀው በሙስሊም ዘገባ ውስጥ የሚገኘው ሶሒሕ ሐዲሥ ይገኝበታል፤ በሐዲሡም ጅብሪል ነብዩን የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ስለ ኢማን ሲጠይቃቸው እንዲህ ብለውታል፦ “ስለኢማን ንገረኝ!” አላቸው። እርሳቸውም 'በአላህ፣ በመላእክቶቹ፣ በመጻሕፍቱ ፣ በመልእክተኞቹ፣ በመጨረሻው ቀንና ልታምን እና በቀደር ክፉም ሆነ ደግ ልታምን ነው።' አሉት።"